Announcement AMC Graduation

AMC Graduation

20th September, 2025

አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ሰልጣኞችን አስመረቀ!

አዲስ አበባ

አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ በተለያዩ ዲፓርትመንቶች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች መስከረም 10 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ። በምረቃው ስነስርዓት ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤን ጨምሮ በርካታ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች እና የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።  

ተመራቂዎቹ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን የሰው ኃይል ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችላቸውን እውቀትና ክህሎት ከኮሌጁ ማግኘታቸው ተገልጿል።

ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በዕለቱ ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት፣ ተመራቂዎች ለሀገር ልማትና ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።  

አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን!

.

Copyright © All rights reserved.

Created with