Announcement የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሱፐርቪዥን ቡድን በአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የማጠቃለያ ምዕራፍ አፈጻጸም ሱፐርቪዥን አካሂዷል፤

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሱፐርቪዥን ቡድን በአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የማጠቃለያ ምዕራፍ አፈጻጸም ሱፐርቪዥን አካሂዷል፤

22nd August, 2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሱፐርቪዥን ቡድን በአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የማጠቃለያ ምዕራፍ አፈጻጸም ሱፐርቪዥን አካሂዷል፤
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ – ሰኔ 20፣ 2017
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሱፐርቪዥን ቡድን አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅን አጠቃላይ የእቅድ አፈጻጸም፣ ተቋማት ግንባታ፣ ቴክኖሎጂ፣አገልግሎት አሰጣጥ፣ ምቹ የስራ ቦታ መፍጠር፣ ብልሹ አሰራር መቅረፍ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት፣ ቅንጅታዊ ስራዎችና የኢኒሼቲቭ ስራዎችን ተመልክቷል፤
በዚህም ቡድኑ በኮሌጁ ውስጥ ያሉ መልካም አፈጻጸሞች፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና የተከናወኑ ተግባራት ከሪፖርት ባለፈ በተቋሙ ያመጡትን ለውጥ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል፤
የሱፐርቪዥን ቡድኑ የኮሌጁ የሆቴል፣ የሬጅስትራር፣ክሊኒክ፣ ደይኬርና የሰራተኞች ካፌ እንዲሁም ወርክሾፖችን በመጎብኘትና ሰራተኞችን በማወያየት የኮሌጁን ነባራዊ ሁኔታ ተገንዝቧል፡፡
ሱፐርቪዥኑ አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ በቀጣይ የተሻለ አቋም ላይ እንዲገኝና የሚጠበቅበትን አገልግሎት መስጠት እንዲችል መፈታት ያለባቸው ችግሮችን በማመላከትና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማመላከት ተጠናቋል፡፡
አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ኮሙኒኬሽን
.

Copyright © All rights reserved.

Created with