Announcement በመትከል ማንሰራራት

በመትከል ማንሰራራት

18th August, 2025

አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ሰራተኞች በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 "አረንጓዴ አሻራቸውን" አኑረዋል
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9/2017 ዓ.ም
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ሰራተኞች ዛሬ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሐግብር በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 "አረንጓዴ አሻራቸውን" አኑረዋል። የኮሌጁ ሰራተኞች ይህንን ተግባር ያከናወኑት "በመትከል ማንሰራራት" በሚለው መሪ ቃል መሰረት ሲሆን፣ አካባቢን የመጠበቅና የማልማት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው። በዚህ የችግኝ ተከላ መርሐግብር የኮሌጁ ሰራተኞች በንቃት በመሳተፍ በወረዳ 05 በሚገኙ ተስማሚ ቦታዎች ላይ 1500 ችግኞችን በመትከል የኮሌጁን ለአረንጓዴ ልማት ያለውን ቁርጠኝነት አሳይተዋል። ይህ ተነሳሽነት በአካባቢው ያለውን አረንጓዴ ልማት ከማሳደግ ባለፈ፣ የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የዚህን መርህ ተፈጻሚነት በማረጋገጥ ለሀገራዊ የአረንጓዴ ልማት የራሱን አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ይገኛል። በመርሐግብሩ ማጠናቀቂያም የኮሌጁ ሰራተኞች የችግኞቹን ስኬታማ እድገት ለማረጋገጥ የማያቋርጥ እንክብካቤ ለማድረግ ቃል ገብተዋል።
‘’ ከፍታን ማፅናት ነገን ማላቅ ‘’
አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

.

Copyright © All rights reserved.

Created with